የሕሙማን መጠለያ ተገነባ
ረቡዕ፣ ሚያዝያ 9 2011ማስታወቂያ
ሕንፃው ለተጠቃሚዎች አገልግሎት ዝግጁ እንዲሆን የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በማሟላት በኩልም የጀርመን ኤምባሲ ልዩ በጀት ሲመድብ የኤምባሲው ባልደረቦች ደግሞ መዋጮ በማደረግ መተባበራቸውን የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ የላከልን ዘገባ ያስረዳል። መጨለያው የተገነባው በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ እና በቃሊቲ የግንባታ ዕቃዎች ማምረቻ ፋብሪካ ትብብር መሆኑም ተገልጿል። የታካሚዎቹ ማረፊያ 52 ሕሙማን ከነአስታማሚዎቹ በጠቅላላ 104 ሰው የማስተናገድ አቅም አለው።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሸዋዬ ለገሠ
ማንተጋፍቶት ስለሺ