የብሬግዚት ዉዝግብ
ዓርብ፣ ጥር 24 2011ማስታወቂያ
ብሪታንያ ከአዉሮጳ ሕብረት አባልነት ያለስምምነት የምትወጣበት መንገድ እየሰፋ መምጣቱን ጉዳዩን የሚከታተሉ ታዛቢዎች እየተናገሩ ነዉ።የአዉሮጳ ሕብረትም፣ ብሪታንያ ያለስምምነት ከሕብረቱ ከወጣች የሚፈጠረዉን ችግር ለማቃለል ይረዳል ያለዉን ሥልት እያጤነ ነዉ።የብሪታንያ ምክር ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ በተለያዩ ጊዜዎች የሚወስንና የሚሽራቸዉ ሐሳቦች ሐገሪቱ ከሕብረቱ አባልነት በአግባቢ ስምምነት ትወጣለች የሚለዉን ተስፋ እያጠበቡት ነዉ። ከዚሕ ቀደም በተያዘዉ ቀጠሮ መሠረት ብሪታንያ በመጪዉ መጋቢት ማብቂያ ከሕብረቱ በይፋ መዉጣት አለባት።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
አዜብ ታደሰ