የትልቆቹ የጀርመን ፖለቲካ ፓርቲዎች እጣ ፈንታ
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 13 2011ማስታወቂያ
ከሁለት ሳምንትም በፊት በሌላው ፌዴራዊ ግዛት ባየር በተካሄደው ምክር ቤታዊ ምርጫ የክርስትያን ሶሻል ህብረት፣ በምህጻሩ ሴ ኤስ ኡ እና ኤስ ፔ ዴ ድጋፍ የሚሰጣቸው ብዙ መራጭ ህዝብ አላገኙም። በአንጻራቸው ትንንሾቹ ፓርቲዎች ቀንቷቸዋል።በሀገሪቱ በአሁኑ ጊዜ የሚሰራበት የፖለቲካ ውክልና ጊዜው ያለፈበት እንደሆነ የሚናገሩት የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት፣ ትልቆቹ ፓርቲዎች የመራጭ ድምፅ እያጡ የመጡበት ሁኔታ መግቻ የሚገኝለት አይመስልም። ትልልቆቹ የጀርመን የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚገኙበት አዳጋች ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
አርያም ተክሌ