1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፈረንሳይ ፖሊስ በበጎ ፍቃደኞች ላይ ጥቃት ያደርሳል ተባለ

ሰኞ፣ ነሐሴ 7 2010

የፈረንሳይ ፖሊስ ለስደተኞች የሰብዓዊ ድጋፍ ለመስጠት በተሰማሩ በጎ ፍቃደኞች ላይ የኃይል ጥቃት እና ወከባ እንደሚፈጽምባቸው ቅሬታ ሲቀርብበት ቆይቷል። በከተሞቹ የሚገኙ አራት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ባለፈው ሳምንት የፖሊስን ድርጊት የሚያወግዝ ጠንከር ያለ ዘገባ ለፈረንሳይ መንግስታዊ የሰብዓዊ መብት ተቋም አቅርበዋል።

https://p.dw.com/p/3364G
Calais Flüchtlingslager
ምስል DW/T.Waldyes

የፈረንሳይ ፖሊስ በበጎ ፍቃደኞች ላይ ጥቃት ያደርሳል ተባለ

ከፈረንሳይ ወደ እንግሊዝ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ መሻገር የሚሹ ስደተኞች በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ ካሌ እና ዳንከርክ ሆነው ዕድላቸውን ይጠባበቃሉ። በእነዚህ ሁለት ከተሞች ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያንን ጨምሮ ቁጥራቸው ከ1000 እስከ 1500 የሚገመቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ቀናትን እያሳለፉ ይገኛሉ። የፈረንሳይ ፖሊስ ለእነዚህ ስደተኞች የሰብዓዊ ድጋፍ ለመስጠት በተሰማሩ በጎ ፍቃደኞች ላይ የኃይል ጥቃት እና ወከባ እንደሚፈጽምባቸው ቅሬታ ሲቀርብበት ቆይቷል።

በከተሞቹ ሰብዓዊ እርዳታ በመስጠት ላይ ያሉ የሚገኙ አራት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ባለፈው ሳምንት የፖሊስን ድርጊት የሚያወግዝ ጠንከር ያለ ዘገባ ለፈረንሳይ መንግስታዊ የሰብዓዊ መብት ተቋም አቅርበዋል። ቅሬታው የቀረበበት የፐርፌ ፓደ ካሌ ግዛት አስተዳደር ግን የማህበራቱን ክስ አጣጥሎታል።

ሙሉ ዘገባ ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።  

ሃይማኖት ጥሩነህ

ተስፋለም ወልደየስ

ሂሩት መለሰ