1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 ድብቅ እስር ቤቶች በትግራይ

ረቡዕ፣ ኅዳር 12 2011

ምክትል ርዕሠ-መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረ-ሚካኤል በቅርቡ በሰጡት መግለጫ «ድብቅ እስር ቤት» የሚባል እንደለሌ አስታዉቀዉ ነበር።አረና ለሉዓላዊነት እና ዴሞክራሲ የተባለዉ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ግን ትግራይ ርዕሠ-ከተማ መቀሌ ዉስጥ ቢያንስ አንድ የድብቅ እስር ቤት መኖሩን እንደሚያዉቁ ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/38frc
Äthiopien Debretsion Gebremichael
ምስል DW/M. Haileselassie

(Beri.Mekelle) Unofficial prisons in Tigray - MP3-Stereo

ሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ መስተዳድር በተለያዩ አካባቢዎች የድብቅ ወይም ሕገ-ወጥ እስር ቤቶች አሉ መባሉ የተለያዩ ወገኖችን እያወዛገበ ነዉ።ምክትል ርዕሠ-መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረ-ሚካኤል በቅርቡ በሰጡት መግለጫ «ድብቅ እስር ቤት» የሚባል እንደለሌ አስታዉቀዉ ነበር።አረና ለሉዓላዊነት እና ዴሞክራሲ የተባለዉ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ግን ትግራይ ርዕሠ-ከተማ መቀሌ ዉስጥ ቢያንስ አንድ የድብቅ እስር ቤት መኖሩን እንደሚያዉቁ ተናግረዋል።በትግራይ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ተጠሪ በበኩላቸዉ የድብቅ እስር ቤት ሥለመኖሩ የደረሰን ጥቆማ የለም ባይ ናቸዉ።

ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ስለሺ