"ጋዜጠኝነት አንደበት ነው" - መላኩብርሃኑ
እሑድ፣ ሰኔ 9 2011ማስታወቂያ
መላኩ በአርቲስት ቲቪ ዓብይ ጉዳይ በሚል እንግዶችን አሳታፊ የውይይት ፕሮግራም በማዘጋጀት ይታወቃል። ከዚህ ቀደም በአዲስ ቲቪ የፖሊስ ፕሮግራም አዘጋጅ ነበር። ለ18 ዓመታት በጋዜጠኝነት ሙያ አገልግሏል። በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃኖች ውስጥ በሙያውና በኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሰርቷል። ጋዜጠኝነት በአጋጣሚ የገባበት ሙያ እንዳልሆነ መላኩ ይናገራል። ሲመኘው የነበረው ሙያ ነበር። የሥነ-ጽሁፍ ፍላጎቱ ወደ ሙያው አስገብቶኛልም ይላል። ጋዜጠኛ ለመሆን የውስጥ ፍላጎት ያስፈልጋል የሚለው መላኩ ብዙ እውነቶችን በጽሁፍ የመግለጽ ችሎታም እንደሆነ ይናገራል። መላኩ የሁለት ልጆች አባትም ነው። የአንድ ሴትና የአንድ ወንድ ልጅ። ተግባቢ መሆኑን እራሱ ስለራሱ ባህሪ ይመሰክራል። በርግጥም ስለራስ መመስከር ከባድ ቢሆንም ይላል መላኩ። ሙሉው ዝግጅት ማገናኛው ላይ ይገኛል
ነጃት ኢብራሂም
አዜብ ታደሰ